<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0"
	xmlns:content="http://purl.org/rss/1.0/modules/content/"
	xmlns:wfw="http://wellformedweb.org/CommentAPI/"
	xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/"
	xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom"
	xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/"
	xmlns:slash="http://purl.org/rss/1.0/modules/slash/"
	>

<channel>
	<title>gaberna-admin &#8211; Gaber Support in North America</title>
	<atom:link href="https://gabersupportnorthamerica.org/author/gaberna-admin/feed/" rel="self" type="application/rss+xml" />
	<link>https://gabersupportnorthamerica.org</link>
	<description>Don&#039;t turn away, Give today!</description>
	<lastBuildDate>Fri, 02 Feb 2024 02:16:49 +0000</lastBuildDate>
	<language>en-US</language>
	<sy:updatePeriod>
	hourly	</sy:updatePeriod>
	<sy:updateFrequency>
	1	</sy:updateFrequency>
	<generator>https://wordpress.org/?v=7.0</generator>

<image>
	<url>https://gabersupportnorthamerica.org/wp-content/uploads/2023/11/cropped-Gaber-Logos-32x32.png</url>
	<title>gaberna-admin &#8211; Gaber Support in North America</title>
	<link>https://gabersupportnorthamerica.org</link>
	<width>32</width>
	<height>32</height>
</image> 
	<item>
		<title>ጋበርን በጨረፍታ</title>
		<link>https://gabersupportnorthamerica.org/%e1%8c%8b%e1%89%a0%e1%88%ad%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8c%a8%e1%88%a8%e1%8d%8d%e1%89%b3/</link>
		
		<dc:creator><![CDATA[gaberna-admin]]></dc:creator>
		<pubDate>Fri, 02 Feb 2024 02:15:31 +0000</pubDate>
				<category><![CDATA[Uncategorized]]></category>
		<guid isPermaLink="false">https://gabersupportnorthamerica.org/?p=960</guid>

					<description><![CDATA[በወረዳችን ኧዣ ስር ሰደው የሚገኙ በርካታ ችግሮችን በመለየት እንዴት መቅረፍ ይቻላል በሚለው ላይ ከበርካታ ተወላጆች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ከተደረጉ በሗላ የበጎ አድራጎት ድርጅት መመስረት እንደሚሻል ታመነበት:: በዋናነት የበጎ አድራጎት ድርጅት [&#8230;]]]></description>
										<content:encoded><![CDATA[
<p class="has-ast-global-color-4-background-color has-background wp-block-paragraph">በወረዳችን ኧዣ ስር ሰደው የሚገኙ በርካታ ችግሮችን በመለየት እንዴት መቅረፍ ይቻላል በሚለው ላይ ከበርካታ ተወላጆች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ከተደረጉ በሗላ የበጎ አድራጎት ድርጅት መመስረት እንደሚሻል ታመነበት::</p>



<p class="wp-block-paragraph">በዋናነት የበጎ አድራጎት ድርጅት የተመረጠበት ምክንያት:</p>



<ol class="wp-block-list">
<li>ችግሮቹ የበዙ በመሆናቸው ባለን ውስን አቅም ብዙሃኑን የሚያሳትፍና ብዙ ዓይነት ስራዎችን ጎን ለጎን መስራት የሚያስችል አደረጃጀት በመፈለግ:</li>



<li>እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ተወላጆች ተሳታፊ እንዲሆኑ :&nbsp; የዓባልነት ክፍያ በመፈፀም ገቢ እዲያስገኙና ቀጣይነት እንዲያረጋግጡ በማሰብ</li>



<li>ባለ ሀብቶች በገንዘብና ሙያተኞች በየሙያቸው በመደራጀት ችግሮችን ለመፍታት ወደ ሗላ እንደማይሉ ተስፋ በማድረግ</li>



<li>ከትላልቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች : ከምርምርና የመንግስት ተቋሟት የዕውቀትና የገንዘብ ድጋፍ ሊገኝ እንደሚችል በማመን ነበር::</li>
</ol>



<p class="wp-block-paragraph">በዚሁ መሠረት ጋበር የበጎ አድራጎት ድርጅት ነሓሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. በመዝገብ ቁጥር 6365 በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ተመዘገቦ ሕጋዊ ሰውነት አገኘ::</p>



<p class="wp-block-paragraph">ጋበር በአንድ ዓመት ተኩል እድሜው ከኧዣ ወረዳ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት:</p>



<ul class="wp-block-list">
<li>በአዲስ አበባ ነዋሪ ከሆኑ ተወላጆች ጋር በጣም ብዙ የግንዛቤ ማስጨበጫና የገቢ ማሰባሰብያ ስብሰባዎችን አካሄዷል : በማካሄድም ላይ ይገኛል::</li>



<li>በወረዳችን ችግሮች ላይ ያተኮረ ውይይት ከወረዳውና ከአገና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር አድርጓል:: ችግሮቹን እጅ ለእጅ ተያይዘን ለመፍታት ቁርጠኛነት መኖሩን አረጋገጠ::</li>



<li>የጋበር ቢሮና የበላይ አመራርን (አንድ ዋና ስራ አስኪያጅ : አንድ የአስተዳደርና ፋይናንስ ኃላፊና አንድ የሞኒተሪንግና መምርያ ኃላፊ) አዋቀረ::</li>



<li>በትምህርት ላይ ያሉትን ችግሮች ለመለየት በከፍተኛ ባለሙያ በመታገዝ ተማሪዎችን : መምህራንን : የትምህርት አመራርን : የወላጅ ኮሚቴን ያካተተ ሰፊ ጥናት አካሄዷል::</li>



<li>ሁለት ጊዜ ከአገና ከተማ አስተዳደርና ከ28ቱ የገበሬ ማህበራት ተወካዮች ጋር በወረዳችን ስር ሠደው&nbsp; በሚገኙ ችግሮችና መፍቻ ዘዴዎቻቸው ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሄዷል::</li>



<li>በሰሜን አሜሪካ ከሚኖሩ የኧዣ ተወላጆች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ጋበር ሠፖርት ግሩፕ ኖርዝ አሜሪካ የተሠኘ ህጋዊ የበጎ አድራጎት ድርጅት ተቋቁሞ አባላት በማሰባሰብና የአባልነት ክፍያ በመሠብሰብ ላይ ይገኛል:: በአውሮፓ ከሚኖሩ ተወላጆች ጋርም ተመሳሳይ አደረጃጀት ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ ነው::</li>



<li>በኣርቲስት አብርሃም ወልዴ እና በባለቤቱ ወ/ሮ ማክዳ ኃ/ሚካኤል&nbsp; በተደረገለዠት የብር 250 ሺህ ልገሳ 450 የብርድልብሶች ገዝቶ ለወገኖቻችን አድሏል::</li>



<li>የጋበር ቴሌግራም ተከታዮች ቁጥር ለማብዛትና ለተማሪዎች መጻህፍት ማሳተሚያ ገንዘብ ለማሰባሰብ በተደረገ ከፍተኛ ጥረት በርካታ ተከታዮች ማፍራትና በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ከሚኖሩ ተወላጆችና ቸር ኢትዮጵያውያን በሚሊዮኖች ገንዘብ ማሰባሰብ ተችሏል::</li>
</ul>



<p class="wp-block-paragraph">*በወረዳው ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ላሉ ሁሉም ተማሪዎች ለ6 የትምህርት ዓይነቶች አንድ መጽሃፍ ለ5 ተማሪዎች መጠቀምያ እንዲሆን አሳትሞ አድሏል::</p>



<ul class="wp-block-list">
<li>በወረዳው ለሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በርካታ የማጣቀሻ መጽሃፍት በእርዳታና በግዥ አግኝቶ አከፋፍሏል</li>



<li>በወረዳው ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ሁሉም ሴት ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የሚያገለግል የንጽህና መጠበቂያ አስመርቶ አከፋፍሏል::</li>



<li>በወረዳው ለሚገኙ 2ኛ ደረጃ እና ለአገና ኢንደስትርያል ኮሌጅ ተማሪዎች በባለሙያ የተዘጋጀ የጥናት ሠነድ መሠረት በማድረግ በስነምግባርና በእውቀት የሚበለጽጉበትን ምክርና ውይይት በየትምህርት ቤታቸው በመገኘት አካሄዷል::</li>



<li>በአንድ ቀን ከመላው የኧዧ ነዋሪዎች ጋር አገር ቤት በየገበሬ ማህበራቸው በመገኘት በችግሮችና መፍቻ ዘዴዎች ላይ የግማሽ ቀን ውይይት አካሄዷል:: በውይይቱም የኧዣን መሠረታዊ ችግሮች ከህብረተሰቡ በግለጽ የተነሱ ሲሆን ለመፍትሄውም ህብረተሰቡን የሚያስተባብሩ : በኣርኣያነታቸው እምነት ያተረፉ ዓባላት ያካተተ ኮሚቴ በሁሉም የቀበሌ ገበሬ ማህበር እንዲቋቋም ተወስናል:: የኮሚቴ ኣባላት ምርጫ የተጠናቀቀ ሲሆን ኃላፊነታቸውን በተመለከተም በቅርቡ የጋራ ውይይት ይካሄዳል::</li>



<li>የወረዳችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉና ብሎም ከፍ የሚያደርጉ በቦርድ ዓባላት የሚመሩ 9 ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ስራ በመግባት ላይ ይገኛሉ::</li>



<li>የ2015 የትምህርት ዘመን አገር አቀፍ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ በቀጥታ ለዩኒቨርስቲና ለሪሜዳል ትምህርት ያለፉትን በትምህርታቸው እንዲበረቱ መክሯል : በባለሙያ የአጠናን ዘዴዎችን አስረድቷል:: የማበረታቻ ስጦታም አድርጓል:: የተቀሩት ተማሪዎችም አገና ኢንዱስትርያል ኮሌጅ ገብተው ስልጠና እንዲወስዱ የቴክኒክ ሙያን ዘርፈ ብዙ ጥቅም አስረድቷል:: ወጣቱ በተለያዩ ሙያዎች በመሳተፍ በአካባቢዬም ሠረቼ ያልፍልኛል የሚል ስሜት እንዲያዳብር ሰፊ ቅስቀሳ ተደርጓል::</li>



<li>በውኃና መስኖ ላይ ጥናት የሚያደርግ የከፍተኛ ሙያተኞች ቡድን ተቋቁሞ ስራ ጀምሯል::</li>



<li>በኧዣና በቤተሰብ ስም የተቋቋሙ ዕድሮች በርካታ ህዝብ ያቀፉ ስለሆኑ ጋበርን የሚደግፉበት ዘዴ ለመቀየስ እድሮችን በተመለከተ አኩሪ ተግባር ከፈፀመው የኧዣ ዕድሮች ህብረት ቢዝነስ አክስዮን ማህበር የቦርድ አመራር ጋር ገንቢ ውይይት አካሄዷል::</li>
</ul>



<p class="wp-block-paragraph">ክብርና ምስጋና በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችሁን ለመርዳት የአቅማችሁን ለምታደርጉ ሁሉ ይሁን::</p>



<p class="wp-block-paragraph"><strong>የጋበር ኣባል ይሁኑ : በገንዘብዎና በሙያዎ ጋበርን በመርዳት እዳዎን ይከፊሉ ::</strong></p>



<p class="wp-block-paragraph"><strong>አቶ ኮሬ ባዌ፤ የጋበር በጎ አድራጎት ድርጅት ሊቀመንበር</strong></p>
]]></content:encoded>
					
		
		
			</item>
		<item>
		<title>Gaber latest news</title>
		<link>https://gabersupportnorthamerica.org/gaber_latest_news/</link>
		
		<dc:creator><![CDATA[gaberna-admin]]></dc:creator>
		<pubDate>Mon, 04 Dec 2023 04:08:47 +0000</pubDate>
				<category><![CDATA[Volunteer]]></category>
		<guid isPermaLink="false">https://gabersupportnorthamerica.org/?p=906</guid>

					<description><![CDATA[&#8220;ጋበር &#8221; የበጎ አድራጎት ማህበር በዚህ ዓመት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች ለያንዳንዳቸው ከ15 ሺህ ብር ጀምሮ በየደረጃው የገንዘብ ድጋፍ አደረገ ።ማህበሩ በህዳር 22፤2016 ዓ።ም ከእዣ ወረዳ አስተዳደር ጋር በመተባበር የ12ኛ [&#8230;]]]></description>
										<content:encoded><![CDATA[
<p class="has-ast-global-color-4-background-color has-background wp-block-paragraph">&#8220;ጋበር &#8221; የበጎ አድራጎት ማህበር በዚህ ዓመት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች ለያንዳንዳቸው ከ15 ሺህ ብር ጀምሮ በየደረጃው የገንዘብ ድጋፍ አደረገ ።<br>ማህበሩ በህዳር 22፤2016 ዓ።ም ከእዣ ወረዳ አስተዳደር ጋር በመተባበር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች የዕውቀትና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል ።<br>የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ መብራቴ ወ/ማርያም እንደገለፁት ጋበር በጎ አድራጎት ማህበር እያከናውናቸው ያሉት ተግባራቶች እንደ እዣ ወረዳ ብሎም እንደ ጉራጌ ዞን የትምህርት ውጤት ስብራትን ለማካካስ ትልቅ አቅም የሚፈጥር በእውቀቱ የዳበረ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል አርዕያ ያለው ተግባር ነው ።<br>ማህበሩ ከሁሉም በላይ ለየት የሚያደርገው የማህበረሰቡ አስተሳሰብ ለመቀየር የጀመረው ተግባር ነው ያሉት ሀላፊው ከአርሶአደር ጀምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በማወያየት በትምህርት በጤና ፡ በግብርናና በሌሎችም ዘርፎች እንዴት መለወጥ እንደሚቻልና ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ ተሞክሮዎችንም ጭምር በተግባር በማሳየት የጀመረው ስራ የሚበረታታ ነውም ብለዋል።<br>ከብዙ ልማቶች ሁሉ ልማት የሚባለው የሰው ልጅ አእምሮ ማልማት መሆኑን ማህበሩ በጥልቀት ተገንዝቦአል ያሉት አቶ መብራቴ በተለይም የተማሪዎች ውጤት ለማሳደግ መፅሀፍቶችን ከመግዛትና ሌሎች በዘርፉ ያሉት ማነቆዎች ለመፍታት እያደረገው ያለው ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንደ ዞኑ እውቅና የሚሰጠውና ተሞክሮ የሚሆንም ጭምር በመሆኑ ምስጋና ይገባቸዋልም ብለዋል።<br>የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዱ ዱላ በዚህም እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ብሎም በወረዳችን የትምህርት ሽፋን ላይ በስፋት ቢሰራም የጥራቱ ጉዳይ በሽፋኑ ልክ ትኩረት ተሰጥቶት ባለመሄዱ ከፍተኛ የሆነ የትምህርት ውጤት ስብራት አጋጥሞናል ብለዋል።<br>በመሆኑም ወረዳችን የዚህ ተፅኖ ተጋሪ ሆኗል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ለዚህም ማሳያ በ2015 ዓም ፈተና ከወሰዱት 448 ተማሪዎች መካከል 28ቶቹ ወደ ዩኒቨርስቲ በቀጥታ የሚገቡ ሲሆን 116 ተማሪዎች ደግሞ የማስተካከያ ትምህርት የሚወስዱ መሆኑንኑንና ሌሎች 330 ወደ ቴክኒክና ሙያ የሚገቡ ናቸው ብለዋል።<br>የገጠመንን የውጤት ስብራትና የትምህርት ቤት መሰረተ ልማት ጉለት ለሟሟላት በተለይም ጋበር የበጎ አድራጎት ማህበር እያደረገው ያለው ከፍተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ድጋፍ በወረዳው ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።<br>የእዣ ወዳ ም/አስተዳዳሪና የትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተጠምቀ በርጋ በበኩላቸው በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ፡ ማህበራዊ ፡ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርግ በስነ ምግባሩ የታነፀ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጋ እንዲሆን በርካታ ቀሪ ስራዎች መስራት እንዳለብን አመላካች ነው ብለዋል።<br>ሀላፊው አክለውም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ የሚተማመን ዜጋ ከማፍራት አኳያ ሰፋፊ ጉለቶች መኖራቸውን በ2014 እና በ2015 የተሰጠው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ጉልህ ማሳያ ነው ።<br>እንደ ወረዳው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎች እና ወደ ቴክኒክና ሙያ ገብተው በአጭር ግዜ እራሳቸውና ሀገራቸው ለመጥቀም ሰፊ እድል ያላቸው ተማሪዎች መልካም ቀሪ ጊዜ እመኛለሁ ያሉት አቶ ተጠምቀ በቀጣይ የትምህርት ባለድርሻ አካላትም በትምህርት ዘርፉ ያሉት ማነቆዎች በቁርጠኝነትና በባለቤትነት በመስራት የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል።<br>የጋበር በጎ አድራጎት ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኮሬ ባዌ በበኩላቸው ድርጅቱ በዋናነት አላማ አድርጎ የተቋቋመው በእዣ ወረዳ ያሉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን መንግስት ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት የአካባቢው ህብረተሰብ በማስተባበር የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችል ነው ብለዋል።<br>በተለይም ድርጅቱ በትምህርት ዘርፍ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት መጽሀፍ ገዝቶ ድጋፍ ከማድረጉም በተጨማሪ በዚህ ዙር በ2015 ዓም ሀገር አቀፍ ፈተና ውስደው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡና በተለያየ መልኩ የማበረታቻ ሽልማት ያዘጋጀ ሲሆን ቀሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ገብተው እንዲማሩ የማስገንዘብ ስራ ለመስራት ነው ብለዋል።</p>



<p class="wp-block-paragraph">ተማሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ጋበር የበጎ አድራጎት ድርጅት ባደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ጠቁመው ይህም ድጋፍ ይበልጥ ውጤታማ ሆነን ለራሳችን ፡ ለአካባቢያችን ብሎም ለሀገራችን እንድጠቅም እገዛ የሚያደርግልን የሞራል ስንቅ ነው ብለዋል ሲል የዘገበው የእዣ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።</p>



<p class="wp-block-paragraph"></p>
]]></content:encoded>
					
		
		
			</item>
	</channel>
</rss>
