<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0"
	xmlns:content="http://purl.org/rss/1.0/modules/content/"
	xmlns:wfw="http://wellformedweb.org/CommentAPI/"
	xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/"
	xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom"
	xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/"
	xmlns:slash="http://purl.org/rss/1.0/modules/slash/"
	>

<channel>
	<title>Uncategorized &#8211; Gaber Support in North America</title>
	<atom:link href="https://gabersupportnorthamerica.org/category/uncategorized/feed/" rel="self" type="application/rss+xml" />
	<link>https://gabersupportnorthamerica.org</link>
	<description>Don&#039;t turn away, Give today!</description>
	<lastBuildDate>Fri, 02 Feb 2024 02:15:32 +0000</lastBuildDate>
	<language>en-US</language>
	<sy:updatePeriod>
	hourly	</sy:updatePeriod>
	<sy:updateFrequency>
	1	</sy:updateFrequency>
	<generator>https://wordpress.org/?v=7.0</generator>

<image>
	<url>https://gabersupportnorthamerica.org/wp-content/uploads/2023/11/cropped-Gaber-Logos-32x32.png</url>
	<title>Uncategorized &#8211; Gaber Support in North America</title>
	<link>https://gabersupportnorthamerica.org</link>
	<width>32</width>
	<height>32</height>
</image> 
	<item>
		<title>ጋበርን በጨረፍታ</title>
		<link>https://gabersupportnorthamerica.org/%e1%8c%8b%e1%89%a0%e1%88%ad%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8c%a8%e1%88%a8%e1%8d%8d%e1%89%b3/</link>
		
		<dc:creator><![CDATA[gaberna-admin]]></dc:creator>
		<pubDate>Fri, 02 Feb 2024 02:15:31 +0000</pubDate>
				<category><![CDATA[Uncategorized]]></category>
		<guid isPermaLink="false">https://gabersupportnorthamerica.org/?p=960</guid>

					<description><![CDATA[በወረዳችን ኧዣ ስር ሰደው የሚገኙ በርካታ ችግሮችን በመለየት እንዴት መቅረፍ ይቻላል በሚለው ላይ ከበርካታ ተወላጆች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ከተደረጉ በሗላ የበጎ አድራጎት ድርጅት መመስረት እንደሚሻል ታመነበት:: በዋናነት የበጎ አድራጎት ድርጅት [&#8230;]]]></description>
										<content:encoded><![CDATA[
<p class="has-ast-global-color-4-background-color has-background wp-block-paragraph">በወረዳችን ኧዣ ስር ሰደው የሚገኙ በርካታ ችግሮችን በመለየት እንዴት መቅረፍ ይቻላል በሚለው ላይ ከበርካታ ተወላጆች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ከተደረጉ በሗላ የበጎ አድራጎት ድርጅት መመስረት እንደሚሻል ታመነበት::</p>



<p class="wp-block-paragraph">በዋናነት የበጎ አድራጎት ድርጅት የተመረጠበት ምክንያት:</p>



<ol class="wp-block-list">
<li>ችግሮቹ የበዙ በመሆናቸው ባለን ውስን አቅም ብዙሃኑን የሚያሳትፍና ብዙ ዓይነት ስራዎችን ጎን ለጎን መስራት የሚያስችል አደረጃጀት በመፈለግ:</li>



<li>እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆኑ ተወላጆች ተሳታፊ እንዲሆኑ :&nbsp; የዓባልነት ክፍያ በመፈፀም ገቢ እዲያስገኙና ቀጣይነት እንዲያረጋግጡ በማሰብ</li>



<li>ባለ ሀብቶች በገንዘብና ሙያተኞች በየሙያቸው በመደራጀት ችግሮችን ለመፍታት ወደ ሗላ እንደማይሉ ተስፋ በማድረግ</li>



<li>ከትላልቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች : ከምርምርና የመንግስት ተቋሟት የዕውቀትና የገንዘብ ድጋፍ ሊገኝ እንደሚችል በማመን ነበር::</li>
</ol>



<p class="wp-block-paragraph">በዚሁ መሠረት ጋበር የበጎ አድራጎት ድርጅት ነሓሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. በመዝገብ ቁጥር 6365 በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ተመዘገቦ ሕጋዊ ሰውነት አገኘ::</p>



<p class="wp-block-paragraph">ጋበር በአንድ ዓመት ተኩል እድሜው ከኧዣ ወረዳ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት:</p>



<ul class="wp-block-list">
<li>በአዲስ አበባ ነዋሪ ከሆኑ ተወላጆች ጋር በጣም ብዙ የግንዛቤ ማስጨበጫና የገቢ ማሰባሰብያ ስብሰባዎችን አካሄዷል : በማካሄድም ላይ ይገኛል::</li>



<li>በወረዳችን ችግሮች ላይ ያተኮረ ውይይት ከወረዳውና ከአገና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር አድርጓል:: ችግሮቹን እጅ ለእጅ ተያይዘን ለመፍታት ቁርጠኛነት መኖሩን አረጋገጠ::</li>



<li>የጋበር ቢሮና የበላይ አመራርን (አንድ ዋና ስራ አስኪያጅ : አንድ የአስተዳደርና ፋይናንስ ኃላፊና አንድ የሞኒተሪንግና መምርያ ኃላፊ) አዋቀረ::</li>



<li>በትምህርት ላይ ያሉትን ችግሮች ለመለየት በከፍተኛ ባለሙያ በመታገዝ ተማሪዎችን : መምህራንን : የትምህርት አመራርን : የወላጅ ኮሚቴን ያካተተ ሰፊ ጥናት አካሄዷል::</li>



<li>ሁለት ጊዜ ከአገና ከተማ አስተዳደርና ከ28ቱ የገበሬ ማህበራት ተወካዮች ጋር በወረዳችን ስር ሠደው&nbsp; በሚገኙ ችግሮችና መፍቻ ዘዴዎቻቸው ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሄዷል::</li>



<li>በሰሜን አሜሪካ ከሚኖሩ የኧዣ ተወላጆች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ጋበር ሠፖርት ግሩፕ ኖርዝ አሜሪካ የተሠኘ ህጋዊ የበጎ አድራጎት ድርጅት ተቋቁሞ አባላት በማሰባሰብና የአባልነት ክፍያ በመሠብሰብ ላይ ይገኛል:: በአውሮፓ ከሚኖሩ ተወላጆች ጋርም ተመሳሳይ አደረጃጀት ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ ነው::</li>



<li>በኣርቲስት አብርሃም ወልዴ እና በባለቤቱ ወ/ሮ ማክዳ ኃ/ሚካኤል&nbsp; በተደረገለዠት የብር 250 ሺህ ልገሳ 450 የብርድልብሶች ገዝቶ ለወገኖቻችን አድሏል::</li>



<li>የጋበር ቴሌግራም ተከታዮች ቁጥር ለማብዛትና ለተማሪዎች መጻህፍት ማሳተሚያ ገንዘብ ለማሰባሰብ በተደረገ ከፍተኛ ጥረት በርካታ ተከታዮች ማፍራትና በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ከሚኖሩ ተወላጆችና ቸር ኢትዮጵያውያን በሚሊዮኖች ገንዘብ ማሰባሰብ ተችሏል::</li>
</ul>



<p class="wp-block-paragraph">*በወረዳው ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ላሉ ሁሉም ተማሪዎች ለ6 የትምህርት ዓይነቶች አንድ መጽሃፍ ለ5 ተማሪዎች መጠቀምያ እንዲሆን አሳትሞ አድሏል::</p>



<ul class="wp-block-list">
<li>በወረዳው ለሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በርካታ የማጣቀሻ መጽሃፍት በእርዳታና በግዥ አግኝቶ አከፋፍሏል</li>



<li>በወረዳው ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ሁሉም ሴት ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የሚያገለግል የንጽህና መጠበቂያ አስመርቶ አከፋፍሏል::</li>



<li>በወረዳው ለሚገኙ 2ኛ ደረጃ እና ለአገና ኢንደስትርያል ኮሌጅ ተማሪዎች በባለሙያ የተዘጋጀ የጥናት ሠነድ መሠረት በማድረግ በስነምግባርና በእውቀት የሚበለጽጉበትን ምክርና ውይይት በየትምህርት ቤታቸው በመገኘት አካሄዷል::</li>



<li>በአንድ ቀን ከመላው የኧዧ ነዋሪዎች ጋር አገር ቤት በየገበሬ ማህበራቸው በመገኘት በችግሮችና መፍቻ ዘዴዎች ላይ የግማሽ ቀን ውይይት አካሄዷል:: በውይይቱም የኧዣን መሠረታዊ ችግሮች ከህብረተሰቡ በግለጽ የተነሱ ሲሆን ለመፍትሄውም ህብረተሰቡን የሚያስተባብሩ : በኣርኣያነታቸው እምነት ያተረፉ ዓባላት ያካተተ ኮሚቴ በሁሉም የቀበሌ ገበሬ ማህበር እንዲቋቋም ተወስናል:: የኮሚቴ ኣባላት ምርጫ የተጠናቀቀ ሲሆን ኃላፊነታቸውን በተመለከተም በቅርቡ የጋራ ውይይት ይካሄዳል::</li>



<li>የወረዳችንን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉና ብሎም ከፍ የሚያደርጉ በቦርድ ዓባላት የሚመሩ 9 ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ስራ በመግባት ላይ ይገኛሉ::</li>



<li>የ2015 የትምህርት ዘመን አገር አቀፍ ፈተና ከተፈተኑ ተማሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ በቀጥታ ለዩኒቨርስቲና ለሪሜዳል ትምህርት ያለፉትን በትምህርታቸው እንዲበረቱ መክሯል : በባለሙያ የአጠናን ዘዴዎችን አስረድቷል:: የማበረታቻ ስጦታም አድርጓል:: የተቀሩት ተማሪዎችም አገና ኢንዱስትርያል ኮሌጅ ገብተው ስልጠና እንዲወስዱ የቴክኒክ ሙያን ዘርፈ ብዙ ጥቅም አስረድቷል:: ወጣቱ በተለያዩ ሙያዎች በመሳተፍ በአካባቢዬም ሠረቼ ያልፍልኛል የሚል ስሜት እንዲያዳብር ሰፊ ቅስቀሳ ተደርጓል::</li>



<li>በውኃና መስኖ ላይ ጥናት የሚያደርግ የከፍተኛ ሙያተኞች ቡድን ተቋቁሞ ስራ ጀምሯል::</li>



<li>በኧዣና በቤተሰብ ስም የተቋቋሙ ዕድሮች በርካታ ህዝብ ያቀፉ ስለሆኑ ጋበርን የሚደግፉበት ዘዴ ለመቀየስ እድሮችን በተመለከተ አኩሪ ተግባር ከፈፀመው የኧዣ ዕድሮች ህብረት ቢዝነስ አክስዮን ማህበር የቦርድ አመራር ጋር ገንቢ ውይይት አካሄዷል::</li>
</ul>



<p class="wp-block-paragraph">ክብርና ምስጋና በችግር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችሁን ለመርዳት የአቅማችሁን ለምታደርጉ ሁሉ ይሁን::</p>



<p class="wp-block-paragraph"><strong>የጋበር ኣባል ይሁኑ : በገንዘብዎና በሙያዎ ጋበርን በመርዳት እዳዎን ይከፊሉ ::</strong></p>



<p class="wp-block-paragraph"><strong>አቶ ኮሬ ባዌ፤ የጋበር በጎ አድራጎት ድርጅት ሊቀመንበር</strong></p>
]]></content:encoded>
					
		
		
			</item>
	</channel>
</rss>
